በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 7 የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስቱሪ ልማት ጽ/ቤት የተከናወኑ ስራዎች ዜና
በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 7 የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስቱሪ ልማት ጽ/ቤት የተከናወኑ ስራዎችን በፎቶ
በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 7 የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስቱሪ ልማት ጽ/ቤት የተከናወኑ ስራዎች በቪዲዮ
በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 7 የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስቱሪ ልማት ጽ/ቤት መግለጫዎች
መንግስት ሀገራችን ከነበረችበት ድህነትና ኋላቀርነት ለማላቀቅ የህብረተሰቡን የኢኮኖሚና ማህበራዊ የላቀ ተሳትፎና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዘርፎችን እየለየና በሂደት ዘርፉን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎችን በመቅረጽና ወደ ተግባር በመግባት ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የበርካታ ዜጎችን የስራ አጥነት ችግር በመቅረፍ ኑሯቸው እንዲሻሻል እየተደረገ ይገኛል፡፡
የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት የዘርፉን አዲስ የልማት ስትራቴጂ ማጽደቅ ተከትሎ በአዲስ መልክ ተደራጅቶ በስትራቴጂው የተቀመጡ ተልዕኮዎችን ለመወጣት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ጽ/ቤቱ በተዋቀረው በእያንዳንዱ የስራ ሂደት መደባዉን ሳይጠብቅ አሁን ባለዉ አደረጃጀት ሊተገበሩ የሚገባቸውን ተግባራት ከከተማው መሪ እቅድና ከዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ በመነሳት ዝርዝር እቅዶችን በማውጣት እየተገበረ ይገኛል፡፡
ጽ/ቤቱ ለተገልጋዮች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻልና ለማቀላጠፍ የተለያዩ ጥረቶችን ሲያደርግ የቆየ ቢሆንም ተገልጋዮች ወደ ጽ/ቤቱ አገልግሎት ለማግኘት ሲመጡ የሚሰጣቸውን የአገልግሎት ዓይነትና ጥራት፤ የሚወስደውን ጊዜ አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያስፈልጋቸው ወጪና እንዲሁም በእነርሱ በኩል ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችን ያመላከተ የተገልጋዮች ቻርተር ማዘጋጀት አስፈላጊ ነው፡፡
አዲስ አበባ ከተማ በ2022 ምቹ የስራ ሁኔታ የተረጋገጠባት ፤ ዘላቂና አስተማማኝ የስራ እድል የፈጠሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆኑ ኢንተርፕራይዞችና ኢንዱስትሪዎች ያደጉባት ከተማ ሆና ማየት ነው ፡፡
የስራ ስምሪት አገልግሎትን በማስፋፋት፤ ሰላማዊ የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነትን በማስፈን ለስራ ፈላጊው ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር፣የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም በመተግበር ከድህነት ወለል በታች የሚገኙ ነዋሪዎችን ኑሮ ማሻሻል እንዲሁም የመስሪያ ቦታ፣ የፋይናንስ፣ የካፒታል ሊዝ፣ የገበያ፣ ቴክኖሎጂ፣ የቴክኒክና ምክር ድጋፍ በማድረግ ኢንተርፕራይዝና አምራች ኢንዱስትሪ በምርትና ምርታማነት ብቁና ተወደዳሪ እንዲሆኑ ማስቻል፡፡
ስራ ፈጣሪነትን ማበረታታት፣
ግልጽና አሳታፊ ተጠያቂነትን ማስፈን፣
ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት፣
ሁልጊዜም ከተግባር መማር፣
የላቀ አገልግሎት መስጠት፣
ፍትሃዊ የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ፣
ፈጣን የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማረጋገጥ፣